ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በሚኖረን ልዩ: የፀሎት ፣ የአምልኮ ፣ የምስክርነት እና የእግዚአብሔርን ቃል የምንማርበት ጊዜ ላይ ተገኝተው አብረውን እግዚአብሔርን እንዲያመልኩ እና የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ ጋብዘኖታል፤ እርሶም ሌሎችን ይጋብዙ!
ዘወትር ማክሰኞ በምናደርገው የፆም እና የፀሎት ጊዜ ነገ ከንጋቱ 10:00 ጀምሮ በቴሌግራም ገፃችን በቀጥታ ስርጭት የጋራ ፀሎት ላይ በመገኘት አብረውን ይፀልዩ ፤ የበረከቱ ተካፋይም ይሁኑ!
ዘወትር ቅዳሜ ከማለዳ 1:00 እስከ 3:00 ስላልዳኑ ነፍሳት ፣ ለቤተሰቦቻችን እና በዙሪያችንም ስላሉት ሁሉ የምንማልድበት ልዩ የምልጃ ጊዜ በመንግስቱ ተልዕኮ አገልግሎት አዘጋጅነት!
"ይህ በእግዚአብሔር በአዳኛችን ፊት ደስ የሚያሰኝ ነው.. እርሱ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑና እውነትን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ ይፈልጋል።
1 ጢሞቴዎስ 2:3-4
በወሩ የመጀመሪያ እሁድ ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ ልዩ የሆነ የፀሎት ፣ የአምልኮ ፣ የመስዋዕት ፣ የምስክርነት ፣ የእግዚአብሔርን ቃል የምንማርበት እና የጌታን እራት የምንወስድበት ጊዜ ይኖረናል። እርሶም በክብር ተጋብዘዋል!
እሁድ ከ4:30 ጀምሮ የመንግስቱ ዘሮች የአገልግሎት ክፍል ልጆችን በእግዚአብሔር ቃል እውነት እያስታጠቀ ይገኛል። ልጆችዎ በእግዚአብሔር ቃል እውነት መንገዳቸው እንዲቃና ፣ ፍፃሜያቸው የከፍታ እና የክብር እንዲሆን ይዘዋቸው ይምጡ።
በሳምንቱ ቀናቶች ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የንጉሡ ቤተሰብ ስብሰባዎች ይደረጋሉ። በእነዚህ ስብሰባዎች ውስጥ የፀሎት ፣ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ፣ የወንጌል ስርጭት እና የምስጋና ጊዜ ይኖረናል። እርሶም የንጉሱ ቤተሰብ አባል ካልሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ።
ይህ የባስ አገልግሎት በነገስታት አገልግሎት የተዘጋጀ ሲሆን ዘወትር እሁድ ለመደበኛ አምልኮ ፕሮግራም ከ 5 (አምስት) የአዲስ አበባ አቅጣጫዎች የሚነሳ እና በ2 ዙር (ጠዋት 2:00 እና 4:00 በሚደርስ) ቅዱሳንን ወደ ቤተክርስቲያን የሚያደርስ እንዲሁም የሚመልስ ይሆናል። ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በቤተክርስቲያኒቱ ስልክ ቁጥር ሊያገኙን ይችላሉ።