Loading...

የቤዛነት አገልግሎት

Kings Ministry Logo

ራዕይ

ድሆችን/ችግረኞችን/ ለክብር መዋጀት


ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።

የያዕቆብ መልእክት 1:27

MOG Abenezer

አገልጋይ ጸጋ ብሩ

የቤዛነት አገልግሎት ዳይሬክተር

ራዕይ

ድሆችን/ችግረኞችን/ ለክብር መዋጀት

ተልዕኮ

ለደሀአደጎች፣ ለመበለቶች፣ ለመጻተኞች ጥላ የሚሆኑ ቅዱሳንን ማስነሳት

ድርሻ

ለቅዱሳን ለመንፈሳዊ ህይወት እድገትና ለውጥ በር/ደጅ/ መሆን

ትስስር

Need/ፍላጎትን/ በሟሟላት መንፈሳቸውን መድረስ

እሴት

  • የቅዱሳን የህይወት ለዉጥ
  • ለችግር ምላሽ መስጠት
  • ጥላ መሆን
  • ፍቅርን መግለጥ
  • ሚስጥር ጠባቂነት
  • እርዳታን በጊዜዉ ማቅረብ
  • ለድንገተኛ ችግር የሚሰጥ አፋጣኝ ምላሽ
የውስጥ ተልዕኮ


በቤተክርስቲያን ለሚገኙ ቅዱሳን የሚያስፈልጋቸውን ድጋፍ በማድረግ እና ጉድለታቸውን በመሙላት ከጎናቸው በመቆም በመንፈሳዊ ህይወታቸው እንዲያድጉ የሚረዳ እንዲሁም የተለያዩ ክህሎቶችን ያዳብሩ ዘንድ የሚረዳ ስልጠና የሚሰጥ የአገልግሎት ክፍል ነው።

የውጭ ተልዕኮ


ቤተክርስቲያን ወይም ቅዱሳን በተለያዩ የማህበረሰብ ተኮር ጉዳይ ላይ እንዲሁም በማህበራዊ እና በአገር አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ከመንግስት እና ከተለያዩ በጎ አድራጊ ተቋማት ጋር አብሮ የሚሰራ የአገልግሎት ክፍል ነው።

Hallelujah Festival

የቤዛነት ኮንፈረንስ

በክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን ከቤዛነት አገልግሎት ጋር በመሆን በየካቲት ወር የሚደረግ አመታዊ ኮንፍረንስ ሲሆን የአገልግሎት ራእይም ድሆችን ለክብር መቤዠት የሚል እንደመሆኑ የኮንፍረንሱ ዋና አላማም ቅዱሳን ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች እንዲኖሩ ረዳት ወይንም ጥላ አድርጎ ማስነሳት ነው።