የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን እሁድ የካቲት 29 ቀን 2012 ዓ.ም "የመንግሥቱን መልዕክት ለትውልድ ሁሉ ማድረስ ፣ የሰማያዊ መንግስትን ህይወት እና ክብርን መግለጥ" የሚልን ራዕይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተቀብላ ሐዋሪያዊ በሆነ ተልዕኮ በመንግስቱ መልዕክተኛ ሐዋሪያ ቅዱስ ተካልኝ የራዕይ ባላደራነት ተመስርታለች። በዚህም ይህንን የመንግስቱን ወንጌል በመስበክ እና የሰማያዊ መንግስት ሚስጥር በማስተማር ላይ ትገኛለች።
የመንግስቱን መልዕክት ለትውልድ ሁሉ ማድረስ የሰማያዊ መንግስትን ሕይወት እና ክብር መግለጥ
መንፈስን እና ኃይልን በመግለጥ ለትውልዱ የመንግስቱን ቃል መስበክ እና ማስተማር
ቤተክርስቲያንን እንደ ሰማያዊ ከተማ በመመስረት እና በመገንባት፤ ቅዱሳንን እንደ ነገስታት እና ካህናት ማሳደግ እንዲሁም እንደ ሰማያዊ ሕዝብ ማስነሳት
የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን መሪ እና የራዕይ ባላደራ
የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን ረዳት መሪ
ራዕዪ ወደ መዳረሻው ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመብረር ሁለት ሰፋፊ የአገልግሎት ክንፎች አሉት፤ እነርሱም የነገስታት አገልግሎት እና የካህናት አገልግሎት ናቸው። የእነዚህ አገልግሎቶች አላማ ቅዱሳንን እንደ ነገስታት እና ካህናት ለመገንባት ነው።