Loading...

ስለ ቤተክርስቲያኒቱ

እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን።

ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1:13-14

ስለ ቤተክርስቲያኒቱ

እንኳን ደህና መጡ!

Church Leader

የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን እሁድ የካቲት 29 ቀን 2012 ዓ.ም "የመንግሥቱን መልዕክት ለትውልድ ሁሉ ማድረስ ፣ የሰማያዊ መንግስትን ህይወት እና ክብርን መግለጥ" የሚልን ራዕይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተቀብላ ሐዋሪያዊ በሆነ ተልዕኮ በመንግስቱ መልዕክተኛ ሐዋሪያ ቅዱስ ተካልኝ የራዕይ ባላደራነት ተመስርታለች። በዚህም ይህንን የመንግስቱን ወንጌል በመስበክ እና የሰማያዊ መንግስት ሚስጥር በማስተማር ላይ ትገኛለች።

ራዕይ

የመንግስቱን መልዕክት ለትውልድ ሁሉ ማድረስ የሰማያዊ መንግስትን ሕይወት እና ክብር መግለጥ

ተልዕኮ

መንፈስን እና ኃይልን በመግለጥ ለትውልዱ የመንግስቱን ቃል መስበክ እና ማስተማር

ቤተክርስቲያንን እንደ ሰማያዊ ከተማ በመመስረት እና በመገንባት፤ ቅዱሳንን እንደ ነገስታት እና ካህናት ማሳደግ እንዲሁም እንደ ሰማያዊ ሕዝብ ማስነሳት

እሴቶች

  • የመንግስቱ ወንጌል
  • የእግዚአብሔርን መንግስት እና ጽድቁን ማስቀደም
  • መንግስታዊ አስተሳሰብ
  • የሰማያዊ ከተማ ስርዓት (አካልነት)
  • የመለኮት አገዛዝ እና ስርዓት
  • ሐዋሪያዊ ተልዕኮ
  • ፍቅር እና ሰላም
  • ቅንነት
  • ለጋስነት
Church Leader

ሐዋርያ ቅዱስ ተካልኝ

የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን መሪ እና የራዕይ ባላደራ

MOG Abenezer

የእግዚአብሔር ሰው አቤኔዘር ማርቆስ

የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን ረዳት መሪ

የክርስቶስ ከተማ ቤተክርስቲያን

ራዕዪ ወደ መዳረሻው ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመብረር ሁለት ሰፋፊ የአገልግሎት ክንፎች አሉት፤ እነርሱም የነገስታት አገልግሎት እና የካህናት አገልግሎት ናቸው። የእነዚህ አገልግሎቶች አላማ ቅዱሳንን እንደ ነገስታት እና ካህናት ለመገንባት ነው።

ዋና የአገልግሎት ክንፎች